Medical Articles & News
በኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ ኤጀንሲ የአርባ ምንጭና የነጌሌ ቦረና ቅርንጫፎች በስራቸው ከሚገኙ የዞን ጤና መምሪያ ሎጅስቲክ ባለሞያዎች ጋር በመድኃኒት አቅርቦት መጠየቂያ ላይ መስከረም 10 ቀን 2014ዓ.ም በሀዋሳ ከተማ ውይይት አካሄደዋል።RRF የጤና ተቋማት የመድኃኒት ፍላጎታቸውን ከኤጀንሲው የሚጠይቁበት ቅፅ ሲሆን የአቅርቦት ሰንሰለቱን ለማሳለጥና ለማጠናከር ከፍተኛ ሚና እነደሚኖረው የነጌሌ ቦረና ስራ አስኪያጅ አቶ ወንድወሰን ማዘንጊያ ገልፀዋል።የውይይቱ ዓላማ ከዞኑ የሎጅስቲክ […]
የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ ኤጀንሲ ለቲቢ ምርመራ አገልግሎት የሚውል መመርመሪያ ኪት ከሀምሌ እስከ መስከረም ባሉት ወራት በተከታታይ እያሰራጨ መሆኑን ከመጋዘን አያያዝና አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡የተሰራጨው መመርመሪያ ኪት ( Urine TB-LAM) የተሰኘ ሲሆን የበሽታ መከላከል አቅማቸው (CD4) ከ200 በታች የሆኑ የኤች አይቪ ህሙማን የቲቢ በሽታ በውስጣቸው መኖር፣ አለመኖሩን በቀላሉ በሽንት ለማረጋገጥ የሚረዳ መመርመሪያ መሆኑንን ለመረዳት ተችሏል፡፡ […]
የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ ኤጀንሲ ከጀርመን መንግስት በድጋፍ የተገኘው የአስትራዜኒካ የኮቪድ-19 የክትባት መድኃኒት የኢፌዴሪ የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ በተገኙበት መስከርም 7ቀን 2013 ዓ.ም ርክክቡ ተካሄዷል፡፡ በድጋፍ የተገኘው የክትባት መድኃኒት 271 ሺህ 200 ደዝ ሲሆን የጀርመን መንግስት ኮቫክስ (COVAX) በተባለ አለም አቀፍ ጥምረት አማካኝነት ለኢትዮጵያ መንግስት የተደረገ ድጋፍ ነው፡፡የጀርመን መንግስት በዓለም ላይ የተከሰተውን የኮቪድ -19 […]
የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ ኤጀንሲ ለጤና ሚኒስቴር በድጋፍ የተገኘውን ለቲቢ ምርመራ አገልግሎት የሚውል የGenexpert ማሽን ጳጉሜ 3 ቀን 2013 ዓ. ም የኢፌድሪ ጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ በተገኙበት ርክክቡ ተካሄዷል።የቲቢ በሽታን ለመቀነስ በሚደረገው ከፍተኛ ጥረት ላይ ስልጠናዎችንና የምርመራ ማሽኖችን ድጋፍ እያደረጉ ላሉ ለUSAIDእና ለአሜሪካ መንግስት ዶ/ር ሊያ ምስጋና አቅርበዋል።የቲቢ በሽታን ለመቀነስና ለመቆጣጠር እንደ ሀገር ለበርካታ […]
በኢትዮጵያ መድሀኒት አቅራቢ ኤጀንሲ እና በኢትዮጵያ #የልብ ህሙማን ህፃናት መረጃ ማዕከል መካከል ከ14 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ ለህፃናት የልብ ህሙማን የሚውሉ የህክምና ግብአቶች የግዥ ውል ጳጉሜ 3 ቀን 2013 ዓ.ም ተፈርመዋል።የህክምና ግብአቶች የሽያጭ ውል ስምምነቱን በኤጀንሲው በኩል ዋና ዳይሬክተሩ ዶ/ር አብዱልቃድር ገልገሎ እና በልብ ህሙማን መርጃ በኩል የማእከሉ ሜድካል ዳይሬክተር ዶ/ር ሳምሶን አደራ ፈርመዋል ።በተደረገው […]
የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ ኤጀንሲ አመራሮችና ሠራተኞችበ”#ጀግንነት ቀን “ለጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊት ጳጉሜ 4 ቀን 2013 ዓ.ም የደም ልገሳ አድርገዋል።ከደም ልገሳው በተጨማሪ አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ለብሄራዊ ክብራችን አኩሪ መስዕዋትነት የሚጠበቅብንን ሁሉ ለመክፈል ከዋና መ/ቤት እስከ ቅርጫፍ የኤጀንሲው ማህበረሰብ ዝግጁ እንደሆኑ ገልጸዋል ። አወል ሀሰን
የተከበራችሁ የሀገራችን ህዝቦች፣ የኤጀንሲያችን ደንበኞች፣ ባለድርሻ እና አጋር አካላት፣ እንዲሁም የተቋማችን ሰራተኞች እና አመራሮች በቅድሚያ እንኳን ለ2014 ዓ.ም አዲስ ዓመት በሰላም፣ በጤና አደረሳችሁ አደረሰን እያልኩ መጪው ዓመት የሰላም፣ የጤና እና የስኬት ዓመት እንዲሆንላችሁ በኢትዮጵያ #መድኃኒት አቅራቢ ኤጀንሲ ስም ልባዊ ምኞቴን ለመግለፅ እወዳለሁ፡፡የዜጎችን ጤንነት ለመጠበቅና ህይወትን ለመታደግ በሚደረገው ርብርብ የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ ኤጀንሲ የማይተካ ሚና እንዳለው […]
በኢትዮጵያ የመድኃኒት አቅራቢ ኤጀንሲ የጎንደር ቅርንጫፍ ባለፈዉ 1 ዓመት #በISO 9001:2015 በጥራት ፖሊሲ መሰረት አሰራሩን ወጥነት ባለዉ መልኩ ሲሰራ ቆይቶ ጳጉሜ 5 ቀን 2013 ዓ.ም የISO 9001:2015 የምስክር ወረቀት ማገኘቱን የቅርጫፉ ስራ አስኪያጅ አቶ እንዳለው አስማማው ገልፀዋል፡፡የለም አቀፍ የጥራት የምስክር ወረቀት መገኘቱ በኤጀንሲው የደንበኞችን እርካታን ለማሳደግ የያዘውን ግብ ለመተግበር ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው ሲሉ ተናግረዋል።ለጎንደር ቅርንጫፍና […]
የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ ኤጀንሲ የ2014ዓ.ም የህፃናትና ጨቅላ ህፃናት ህክምና አገልግሎት የሚውሉ ግብዓቶች ምጠና ወርክሾፕ ከግንቦት 23 እስከ 26 ቀን 2013 ዓ.ም በአዳማ ከተማ እያካሄደ ይገኛል ። ወርክሾፑ በጤና ሚኒስቴር ቅድሚያ ተሰጥቶት እየተሰራ ባለው የጤና ፖሊሲ መሰረት የህፃናትንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ የሚውሉ ግብዓቶችን ለ2014 በጀት ዓመት ግዥ ምጠና ለማካሄድ እንደሆነ የኤጀንሲው የእናቶችና ህፃናት ጤና ግብዓት […]