የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ ኤጀንሲው በዘላቂ የልማት ግቦች /SDGs/ በጀት የተገዛውን የፀረ -ወባ ኬሚካል ከግንቦት ወር ጀምሮ ማሰራጨቱን ከመጋዘን አያያዝና አስተዳደር ዳይሬክቶሬት የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡ኬሚካሉ የወባ ትንኝ የምታስተላልፈውን የወባ በሽታን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ከምንጠቀምባቸው መከላከያ መንገዶች አንዱ እንደሆነ የተገለፀ ሲሆን በየቤት ውስጥ የሚረጭ 215 ሺህ 162.4 ኪ.ግ መሰራጨቱ ተገልጿል፡፡ስርጭቱም በኤጀንሲው ቅርንጫፎች አማካኝነት ለትግራይ፣ለአፋር፣ ለደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች፣ […]