የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት (EPSS) አዲሱን አዋጅ ተከትሎ ወደ ትግበራ የገባውን "ውል የተገባለት የአቅርቦት ሥርዓት" (Committed Demand & Supply System_CDSS) አፈጻጸም ከቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጆችና ከዳይሬክተሮች ጋር በጋራ ገመገመ።
በግምገማው ወቅት የሦስቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተሮች የገለጹዋቸው ዋና ዋና ነጥቦች፦
🔹 አቶ ታሪኩ በላቸው፦ "የሕክምና ግብዓት አቅርቦት መቆራረጥን በዘላቂነት ለመፍታት ይህ ሥርዓት በ2018 ዓ.ም የጀመርነው ቁልፍ ስራችን ነው፤ በአቅርቦት ሰንሰለቱ ላይ ያሉ ሁሉም አካላት ኃላፊነታቸውን በአግባቡ መወጣት አለባቸው።"
🔹 አቶ አቅናው ካውዛ፦ "በዚህ ዓመት የሕክምና ግብዓቶች አቅርቦት ምጣኔ ትልቅ መሻሻል አሳይቷል። ሥርዓቱ በአቅርቦት ሰንሰለቱ ላይ የመረጃ ግልጸኝነት (Transparency) እንዲሰፍን ከፍተኛ እገዛ አድርጓል።"
🔹 አቶ ሰለሞን ንጉሴ፦ "ሥርዓቱ በአገልግሎቱ እና በጤና ተቋማት መካከል ያለውን የመድኃኒት መገኘት ምጣኔ (Availability) ተቀራራቢ እንዲሆን አድርጎታል። በቀጣይም ይበልጥ ውጤታማ ለመሆን የዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ ነው።"
የሥርዓቱ (CDSS) ዋና ዋና ጥቅሞች፦
✅ የአቅርቦት መቆራረጥን በዘላቂነት መፍታቱ፤
✅ በየደረጃው ያሉ አካላትን ተጠያቂነትና የሥራ ድርሻ በዝርዝር ማስቀመጡ፤
✅ የቅርንጫፎችን ብቃት ለመመዘን የሚያስችል ቁልፍ የአፈጻጸም መለኪያ (KPI) መዘጋጀቱ።
✅ በውል ተዋዋዮች መካከል እኩል ተጠያቁነት የሚያሠፍን መሆኑ
✅ አስገዳጅ በሆነ የህግ ማእቀፍ ውስጥ መተግበሩ
አገልግሎቱ በቀጣይም የጤና ተቋማት የሚፈልጉትን ግብዓት በወቅቱና በጥራት እንዲያገኙ በትኩረት እንደሚሠራ አረጋግጧል።
#ማገልገል_ክብር_ነው! 🇪🇹
#EPSS
ማህሌት አበራ