የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ለሰማዕት ሠራተኛው ቤተሰብ ቤት አስረከበ። ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
News
February 23, 2026
69 views

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ለሰማዕት ሠራተኛው ቤተሰብ ቤት አስረከበ። ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

በዚሁ መሠረት በሰሜኑ ጦርነት ወቅት በሥራ ገበታቸው ላይ እያሉ ሕይወታቸውን ላጡት የደሴ ቅርንጫፍ የጥበቃ ሠራተኛ አቶ ቻለው ሸዋንግዛው፣ ተቋሙ የመኖሪያ ቤት ግንባታ በማከናወን ለቤተሰቦቻቸው አስረክቧል።

የተደረጉ ዋና ዋና ድጋፎች፦

#የመኖሪያ ቤት ስጦታ፦ የሟች ቤተሰቦች ከኪራይ ቤት ወጥተው የራሳቸው ቋሚ መጠለያ እንዲኖራቸው ተደርጓል ።

#የሥራ ዕድል ፈጠራ፦ የሟች ቤተሰቦች እንደ የትምህርት ደረጃቸውና እንደ ሙያቸው በተቋሙ ውስጥ የሥራ ዕድል እንደሚመቻችላቸው ቃል ተገብቷል ።

#ቀጣይነት ያለው ክትትል፦ ተቋሙ ለቤተሰቡ አስፈላጊውን ድጋፍ ማድረጉን እንደሚቀጥል ተረጋግጧል።

አቶ ታሪኩ በላቸው አክለውም፣ ተቋሙ ለሠራተኞቹ የሚያደርገውን መሰል ድጋፎች አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።

በመኖሪያ ቤት ርክክብ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የወረዳውና የከተማ አስተዳደሩ የሥራ ኃላፊዎች፣ የተቋሙ ዳይሬክተሮችና ሠራተኞች በተገኙበት ቤቱ ለወይዘሮ መሬማ ሀሰን ተረክቧል።

#ማገልገል ክብር ነው!
Share this article:
🤖
EPSS Assistant Online · Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service